የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

Commissioner Image

የተከበራችሁ ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ መላው የሃገራችን ፖሊስ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋር የፀጥታ አካላት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች።

ዝርዝር መልዕክት

አዳዲስ ዜናዎች!

  • ከኢትዮጵያ ፖሊስ፣ ከሪፐብሊካን ጋርድ ጥበቃ ኃይልና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች በቻይና ሀገር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ( Federal News)

    ቻይና ቤጂንግ፣ መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)  ከኢትዮጵያ ፖሊስ፣ ከሪፓብሊካን ጋርድ ጥበቃ ኃይል፣ ከኢትዮጵያ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ እና ከኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች በቻይና ሪፐብሊክ ወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።

    ክቡር የቻይና ሪፐብሊክ ወንጀል ምርመራ የፖሊስ ዪኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንት ዊ ሸንግዋንግ በስልጠና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የፖሊስ ሥልጠና መርሃ ግብሩ በኢትዮጵያና በቻይና የፖሊስ ተቋማት መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ የነበረውን መልካም ግንኙነትና ተግባቦት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ገልፀዋል።

  • ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት የበዓል ስጦታ ተበረከተላቸው( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት ለማስፈን በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች ተሰማርተው ከፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በጀግንነት ሲፋለሙ ጉዳት ደርሶባቸው በፖሊስ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ ለሚገኙ የፌደራልና የክልል ፖሊስ አመራሮችና አባላት የበዓል ስጦታ ተበረከተላቸው።

  • “በደም በአጥንታቸው ሀገርን አፅንተው ሉዓላዊት ሀገር ለአስረከቡን ምስጋና ይገባቸዋል” ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3 ቀን 2016 ዓ.ም ኢ.ፌ.ፖ.ሚ፡- የሉዓላዊነት ቀን “ኅብር ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመላ ሀገሪቱ ተከበረ፡፡

  • የቻይና የሕዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር ለክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የGreat Wall Commemorative Gold Medal Award አበረከተ( Federal News)

    ቻይና ቤጂንግ፣ ጳጉሜ 02 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የቻይና የሕዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር ለክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የ Great Wall Commemorative Gold Medal Award አበረከተ፡፡

  • በሽብርና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም ሦስት ጊዜ የሞት( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) በሽብርና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ ከ1989 ዓ ም ጀምሮ እሰከ 1999 ዓ ም በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም ሦስት ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ።

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል ባላቸው ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀመረ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል ባላቸው ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀመረ።

የሚሰጡ አገልግሎቶች

የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች


  1. ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
  2. የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
  2. ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት


በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
  2. የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት


በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች


በክስ መቀበል አገልግሎት

  1. የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
  2. የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣